የሁለገቡ ከያኒ ነቢይ መኮንን የቀብር ሥነሥርዓት ነገ በናዝሬት ይፈጸማል• በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ የስን…

Reading Time: < 1 minute
*
የሁለገቡ ከያኒ ነቢይ መኮንን የቀብር ሥነሥርዓት ነገ በናዝሬት ይፈጸማል

• በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ የስንብት መርሃ ግብር ይካሄዳል

በናዝሬት- አዳማ አፈር ፈጭቶ ያደገውና ፊደል ቆጥሮ የተማረው አንጋፋው የጥበብ ባለሙያ ነቢይ መኮንን፣ በህይወቱ ፍጻሜ ላይ ለዘላለም ሊያርፍበት የመረጠው ቤት የእናቱን ነው ተብሏል፡፡

ቤተሰቦቹ እንደገለጹት፣ ነቢይ መኮንን ዛሬ ማለዳ ለዘላለም ከማሸለቡ በፊት በተናገረው የመጨረሻ ቃሉ፤ “በምወዳት ከተማዬ ናዝሬት፣ ከምወዳት እናቴ ማረፊያ ቅድስት ማርያም ቤ/ክርስቲያን ቅበሩኝ” ብሏል፡፡

በዚሁ መሰረት፣ የሁለገቡ ከያኒ ነቢይ መኮንን የቀብር ሥነስርዓት፣ ነገ ሐሙስ ሰኔ 27 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ በ9 ሰዓት፣ በአዳማ/ናዝሬት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን እንደሚፈጸም ታውቋል፡፡

ከዚያ አስቀድሞ ግን በነገው ዕለት ሐሙስ ከረፋዱ 3፡30 – 4 ሰዓት በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ፣ አንጋፋ የኪነጥበብ ሙያ አጋሮቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት የስንብት መርሃ ግብር ይከናወናል፡፡
143900cookie-checkየሁለገቡ ከያኒ ነቢይ መኮንን የቀብር ሥነሥርዓት ነገ በናዝሬት ይፈጸማል• በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ የስን…

Share to...

Facebook
Telegram
WhatsApp
Twitter
Email
Print
ጌች ሐበሻ

ጌች ሐበሻ

ጌትነት ተመስገን (ጌች ሐበሻ) በማኀበራዊ ጉዳዮች እና ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመጻፍ ንቁ ተሳታፊ ነው።
ጌች ሐበሻ

ጌች ሐበሻ

ጌትነት ተመስገን (ጌች ሐበሻ) በማኀበራዊ ጉዳዮች እና ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመጻፍ ንቁ ተሳታፊ ነው።

Any Thought?

Be part of the Community! Comment, connect, spread some joy and let the fun begin!

YOU MAY ALSO LIKE