ማሚላ ሉቃስ “እንደ ጊዜው” አልበም ለቀቀተወዳጁ ሙዚቀኛ ማሚላ ሉቃስ የራሱ ያለውን የበኩር አልበሙን አንጋፋ…

*
ማሚላ ሉቃስ “እንደ ጊዜው” አልበም ለቀቀ

ተወዳጁ ሙዚቀኛ ማሚላ ሉቃስ የራሱ ያለውን የበኩር አልበሙን አንጋፋ ስመጥር ባለሞያዎች የተሳተፉበት እና የተለያየ የሙዚቃ ጣዕም በውስጡ ያለው “እንደ ግዜው” አልበም በዛሬ እለት በጥር 30/2017 አመተ ምህረት ወቷል፡፡

አስራ ሶስት ትራኮችን ያለው “እንደ ግዜዉ” አልበም አንጋፋ እና ወጣት ባለሞያዎች ተሳትፈዉበታል በግጥምና ዜማ ይልማ ገ/አብ ፣ ናትናኤል ግርማቸዉ ፣ አለማየሁ ደመቀ፣ ፍሬዘር አበበ ወርቅ  እንዲሁም ራሱ ድምፃዊ ማሚላ ሉቃስን ጨምሮ ሌሎችም በርካታ ባለሙያዎች አሻራቸዉን አሳርፈዉበታል፡፡ በሙዚቃ ስልተምት ሬጌ ፣አፍሮ ቢት፣ችክችካ እና የመሳሰሉት እንዳሉበት ገልጿል፡፡

አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ ፣ ካሙዙ ካሳ ፣ ሚካኤል ሀይሉ (ሚኪ ጃኖ) ፣ ስማገኘዉ ሳሙኤል ፣ ፋኑ ጊዳቦ ፣ ሱራፌል የሺጥላ እና ጊልዶ ካሳ በሙዚቃ ቅንብሩ ተሳትፈዉበታል፡፡

አልበሙ ዛሬ ጥር 30 ጀምሮ በሰዋሰዉ አፕ እና በሰዋሰዉ የዩቲዩብ ገፅ ላይ ተለቋል ገብታችሁ አጣጥሙ፡፡
173690cookie-checkማሚላ ሉቃስ “እንደ ጊዜው” አልበም ለቀቀተወዳጁ ሙዚቀኛ ማሚላ ሉቃስ የራሱ ያለውን የበኩር አልበሙን አንጋፋ…

Share to...

Facebook
Telegram
WhatsApp
Twitter
Email
Print

Any Thought?

Be part of the Community! Comment, connect, spread some joy and let the fun begin!

YOU MAY ALSO LIKE