ሁልጊዜ ታክሲ ውስጥ ሒሳብ ሰብስቡልኝ ሲል ሁለት ነገር ወደ አእምሮዬ ይመጣልአንደኛው ሹፌሩን መተባበር መልካ…

Reading Time: < 1 minute
ሁልጊዜ ታክሲ ውስጥ ሒሳብ ሰብስቡልኝ ሲል ሁለት ነገር ወደ አእምሮዬ ይመጣል

አንደኛው ሹፌሩን መተባበር መልካም መሆኑን
ሁለተኛው ግን ቆይ ለምን አንድ ዜጋ ይዞ አይሠራም?

ይህ ሰው እኮ ሁሌም ገንዘብ ስለምንሰበስብለት አብሮት ሊሠራ የሚችል የአንድ ወጣት ዜጋ ሥራ ቀምተን ሥራ አጥ አድርገናል ማለት ነው።

እኔ ዛሬ ሒሳብ በመሰብሰብ ስለተባበርሁት ነገ ሌላው ሰው እንዲተባበረውም መዘዝ እያመጣሁበት ነው ያ ሰው ደግሞ ሒሳብ ሰብስቦ ስለማያውቅ እስከመጨነቅ ይደርሳል። ከዚህም አልፎ ከሌላ ሰው ጋር እስከመጣላት ይደርሳል አብረን ተሳፍረን አንዱ ሒሳብ ሰብሳቢ ሆኖ አብረውት ከተሳፈሩት ሰዎች ጋር እስከመጣላት ሲደርሱ አይቻለሁ!

ብር ሰብስቡልኝ ገመዱን ጎትተ፣  ሽቦውን ንካው፣ ወደ ታች ተጫንና ክፈተው፣ የት ናችሁ ? ብለህ አስገባልኝ ወዘተ የሚሉ መመሪያዎችን እያስተላለፈ፣ ዝርዝር ለመስጠት በሁለት እጁ ብር እየቆጠረም መኪና እያሽከረከረ፣ ሒሳብ አብሮ እየሠራ አብረነው የምንሠራለት ሹፌር እኛ ስላገዝነው ብቻ የአንድ ወጣት ዜጋ ሥራ የቀማን ይመስለኛል።

እኛ ሹፌሩን እየተባበርን ነው መልካም ተግባር ነው  ግን የአንድ ዜጋ ሥራ እየቀማን ነው እኒህ ያለ እረዳት የሚሠሩ ሹፌሮችን ውጤታማነት የሚያዩ ሌሎችም የታክሲ ሹፌሮች አሁን አሁን ያለ ረዳት መሥራቱን እየተቀላቀሉ ታክሲዎች ሁሉ ረዳት እየተዉ ሕዝቡ እረዳት እየሆነ ነው 2 ሺህ ታክሲዎች ያለ ረዳት ሠሩ ማለት 2ሺህ ወጣቶች ሥራ አልባ ሆኑ ማለት ነው በዚህ ውስጥ ደግሞ ሌላ ቤተሰብ አለ

በእርግጥ አንዳንድ ሹፌሮች ደግሞ ለምን ረዳት አይኖራችሁም ሲባሉ የሚነግሩን ምላሽ በቃ አልቻልናቸውም ያጭበረብሩናል የነዳጅ ዋጋ ምናምን ይላሉ።

ምንም ቢሆን በአግባብ ሠርቶ መለወጥ እንጂ ትርፋማነትን በተሳሳተ መንገድ ለማግኘት መሞከር ስሕተት ነው ለአሽከርካሪና ለተሳፊሪዎችም ስልክ እያወሩ ከመንዳት በላይ አደጋ ያስከትላል የዜጋ ሥራ አጥነትንም ያስፋፋል ብዬ ነው የማስበው።

እኔ ሁሌም ገንዘብ ሰብስቡልኝ የምትለዋን ንግግር ስሰማ እኒህ ሁለት ሐሳቦች ወደ አእምሮዬ መምጣታቸው አይቀርም

እናንተስ ምን ትላላችሁ?

Via Zelalem Hasebe
181800cookie-checkሁልጊዜ ታክሲ ውስጥ ሒሳብ ሰብስቡልኝ ሲል ሁለት ነገር ወደ አእምሮዬ ይመጣልአንደኛው ሹፌሩን መተባበር መልካ…

Share to...

Facebook
Telegram
WhatsApp
Twitter
Email
Print
ጌች ሐበሻ

ጌች ሐበሻ

ጌትነት ተመስገን (ጌች ሐበሻ) በማኀበራዊ ጉዳዮች እና ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመጻፍ ንቁ ተሳታፊ ነው።
ጌች ሐበሻ

ጌች ሐበሻ

ጌትነት ተመስገን (ጌች ሐበሻ) በማኀበራዊ ጉዳዮች እና ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመጻፍ ንቁ ተሳታፊ ነው።

Any Thought?

Be part of the Community! Comment, connect, spread some joy and let the fun begin!

YOU MAY ALSO LIKE