በ2030 ዓ.ም ወደ ውጭ የሚሄደውን ህክምና ሙሉ
በሙሉ አስቀርቶ ማየት እንዲሁም በአይነቱም ሆነ በይዘቱ ከምስራቅ አፍሪካ ቁጥር አንድ ተመራጭ ተርሸሪ ሆስፒታል ሆኖ ማየትን ራዕይን አንግቦ የተመሠረተው ሐመር ተሪሸሪ ሆስፒታል የአክሲዮን ሽያጭ መጀመሩን ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2015 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን ተቋማት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አሳወቃል።

አክሲዮን ማህበሩ በ17 የህክምና ባለሙያዎች አደራጅነት የተቋቋመ ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ የሚገነባው ሆስፒታል አጠቃላይ ወጪው ሁለት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር እንደሆነ አክሲዮን ማህበር አደራጅ የቦርድ ፕሬዝዳንት ዶክተር ዳንኤል አዱኛ የገለጹ ሲሆን ሆስፒታሉ ከስድስት ወር በኋላ በኪራይ ህንፃ ላይ ስራ እንደሚጀምር ገልጸዋል።

የአክሲዮን ሽያጩ የፊታችን ነሐሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ በአማራ ባንክ ፣ በአዋሽ ባንክ በአቢሲኒያ ባንክ እና በዳሽን ባንክ ሽያጭ የሚጀምር ሲሆን ለአንድ ወር ያክል አክሲዮን ለሚገዙ የመስራችነት እድል እንደሚያገኙ ዶክተር ዳንኤል አዱኛ ጨምረው ገልጸዋል።
![]()

በ 34 ሚልየን ብር በተከፈለ ካፒታል የተመሰረተው አክሲዮን ማህበር ፤ የአንድ አክስዮን ዋጋው 1,000 ብር ሲሆን መግዛት የሚቻለው ትንሹ የአክስዮን ብዛት ሃምሳ ሲሆን ትልቁ ደግሞ መቶ ሺህ አክስዮን መሆኑን አደራጅ ኮሚቴው አሳውቀዋል።
562900cookie-checkሐመር ተሪሸሪ ሆስፒታል የአክሲዮን ሽያጭ መጀመሩን አበሰረ።no
በሙሉ አስቀርቶ ማየት እንዲሁም በአይነቱም ሆነ በይዘቱ ከምስራቅ አፍሪካ ቁጥር አንድ ተመራጭ ተርሸሪ ሆስፒታል ሆኖ ማየትን ራዕይን አንግቦ የተመሠረተው ሐመር ተሪሸሪ ሆስፒታል የአክሲዮን ሽያጭ መጀመሩን ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2015 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን ተቋማት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አሳወቃል።

አክሲዮን ማህበሩ በ17 የህክምና ባለሙያዎች አደራጅነት የተቋቋመ ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ የሚገነባው ሆስፒታል አጠቃላይ ወጪው ሁለት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር እንደሆነ አክሲዮን ማህበር አደራጅ የቦርድ ፕሬዝዳንት ዶክተር ዳንኤል አዱኛ የገለጹ ሲሆን ሆስፒታሉ ከስድስት ወር በኋላ በኪራይ ህንፃ ላይ ስራ እንደሚጀምር ገልጸዋል።

የአክሲዮን ሽያጩ የፊታችን ነሐሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ በአማራ ባንክ ፣ በአዋሽ ባንክ በአቢሲኒያ ባንክ እና በዳሽን ባንክ ሽያጭ የሚጀምር ሲሆን ለአንድ ወር ያክል አክሲዮን ለሚገዙ የመስራችነት እድል እንደሚያገኙ ዶክተር ዳንኤል አዱኛ ጨምረው ገልጸዋል።

በ 34 ሚልየን ብር በተከፈለ ካፒታል የተመሰረተው አክሲዮን ማህበር ፤ የአንድ አክስዮን ዋጋው 1,000 ብር ሲሆን መግዛት የሚቻለው ትንሹ የአክስዮን ብዛት ሃምሳ ሲሆን ትልቁ ደግሞ መቶ ሺህ አክስዮን መሆኑን አደራጅ ኮሚቴው አሳውቀዋል።











