ለቱ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኀብረት ስራ ማኀበር አዲሱን አርማ አስተዋወቀለቱ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት…

Reading Time: < 1 minute
*
ለቱ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኀብረት ስራ ማኀበር አዲሱን አርማ አስተዋወቀ

ለቱ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር በ2015 ዓ.ም በ200 መስራች አባላት የተቋቋመ ሲሆን የአባላትን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ አስተዋፅኦ ለማሳደግ የተመሰረተ ሲሆን ስራ በጀመረ 6 ወራት ውስጥ ከ32 ሚሊዮን ብር በላይ ቁጠባ መሰብሰቡን ገልጿል።

የኅብረት ሥራ ማህበሩ ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር በ6 ወር ውስጥ መስጠቱና የአባላት ብዛት ከ1600 መብለጡን ባካሄደው አዲስ አርማ የማስተዋወቅ መድረክ ላይ ተገልጿል።



በእለቱ የሀይማኖት አባቶች ፣ የኅብረት ሥራ ማህበር አባላት፣ ታዋቂ ሰዎች በእለቱ ተገኝተው መርሃ ግብሩን የተከታተሉ ሲሆን ተቋሙ ከዚህ በላይ መስራት እንድሚጠበቅበት ተገልጿል።

በእለቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረገቱ የለቱ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ዋና ስራ አቶ አዱኛ ገረሙ ማህበሩን ለየት የሚያደርገው ለሚቆጥቡት ደንበኞች የተሻለ ወለድ መክፈሉና የብዙሃኑ ደንበኞች ፍላጎትና ጥያቄ የሆነውን የቤትና መኪና ግዢ ብድር አገልግሎት በ4 ወር ጊዜ ውስጥ ብድር መስጠት መቻሉ ነው ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የደንበኞቻችን የቁጠባ ባህል ለማሳደግ ሲባል ከፍተኛ የሆነ የቁጠባ ወለድ ምጣኔ መክፈሉ ማህብሩን ከሌሎች መሰል ማህበራት በብዙሃኑ ዘንድ ተመራጭ ያደርገናል በማለት አክለዋል።

https://1234.getutemesgen.et/uploads/Kb34vCxP.jpg

ለቱ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር በፍጥነት እያደገ የሚገኝ የኅብረት ሥራ ማህበር ሲሆን የዚህ ማህበር ጥቅም ተጋሪ ለመሆን ፍላጎት ያላቸው ግለሰቦችተቋማትና ሌሎችም የማህበሩ አባል መሆን እንድሚችሉ መልእክት ተላልፏል።
170940cookie-checkለቱ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኀብረት ስራ ማኀበር አዲሱን አርማ አስተዋወቀለቱ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት…

Share to...

Facebook
Telegram
WhatsApp
Twitter
Email
Print
ጌች ሐበሻ

ጌች ሐበሻ

ጌትነት ተመስገን (ጌች ሐበሻ) በማኀበራዊ ጉዳዮች እና ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመጻፍ ንቁ ተሳታፊ ነው።
ጌች ሐበሻ

ጌች ሐበሻ

ጌትነት ተመስገን (ጌች ሐበሻ) በማኀበራዊ ጉዳዮች እና ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመጻፍ ንቁ ተሳታፊ ነው።

Any Thought?

Be part of the Community! Comment, connect, spread some joy and let the fun begin!

YOU MAY ALSO LIKE