ታላቅ የሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ምረቃ በዓል
“በዚያን ጊዜ አፋችን ደስታን፥ አንደበታችንም ሐሴትን ሞላ፤ በዚያን ጊዜ በአሕዛብ ዘንድ፦ “እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገላቸው፡” ተባለ። እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገልን፥ ደስም አለን።” መዝ 126 ፥3
በሰሜን አሜሪካ በቨርጂንያ ግዛት በአሌክሳንደርያ ከተማ የሚገኘው የምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በተመሠረተ በጥቂት ዓመታት ውስጥ በፈቃደ እግዚአብሔር በዲሲ ፣ ሜሪላንድና ቨርጂኒያ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን የተዋሕዶ ልጆች ምዕመናን መጽናኛ የሚሆን ግዙፍ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በ 3.1 Million USD ተገዝቶ የቁልፍ ርክክብ መደረጉ ይታወቃል።
ስለሆነም ይህ ታላቅ ሕንጻ ቤተክርስቲያን የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጰጳሳትና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ ሊቃውንት በተገኙበት የፊታችን ቅዳሜ ታኅሣስ 26/2017 ዓ.ም (Sat, Jan 04/2025) በሀገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ 4:00PM ጀምሮ ቤተክርስቲያኑ ይባረካል።
እሁድ ታኅሣስ 27/2017 ዓ.ም (Sun, Jan, 05/2025) በሀገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከሌሊቱ 1:00 AM ጀምሮ ሥርዓተ ማኅሌቱና የቅዳሴ ቤቱ በዓል ስለሚከበር ከላይ በተጠቀሱት ታሪካዊ ቀናት የተዋሕዶ ልጆች ምዕመናን ሁላችሁም በቦታው (2912 King St Alexandria VA 22302) ተገኝታችሁ በዓሉን እንድታከብሩ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም ጥሪያችንን እናቀርባለን ::
ሰላመ እግዚአብሔር አይለየን
መልአከ ገነት ቀሲስ ጥላሁን አበበ
የደብሩ አስተዳዳሪ
“በዚያን ጊዜ አፋችን ደስታን፥ አንደበታችንም ሐሴትን ሞላ፤ በዚያን ጊዜ በአሕዛብ ዘንድ፦ “እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገላቸው፡” ተባለ። እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገልን፥ ደስም አለን።” መዝ 126 ፥3
በሰሜን አሜሪካ በቨርጂንያ ግዛት በአሌክሳንደርያ ከተማ የሚገኘው የምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በተመሠረተ በጥቂት ዓመታት ውስጥ በፈቃደ እግዚአብሔር በዲሲ ፣ ሜሪላንድና ቨርጂኒያ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን የተዋሕዶ ልጆች ምዕመናን መጽናኛ የሚሆን ግዙፍ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በ 3.1 Million USD ተገዝቶ የቁልፍ ርክክብ መደረጉ ይታወቃል።
ስለሆነም ይህ ታላቅ ሕንጻ ቤተክርስቲያን የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጰጳሳትና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ ሊቃውንት በተገኙበት የፊታችን ቅዳሜ ታኅሣስ 26/2017 ዓ.ም (Sat, Jan 04/2025) በሀገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ 4:00PM ጀምሮ ቤተክርስቲያኑ ይባረካል።
እሁድ ታኅሣስ 27/2017 ዓ.ም (Sun, Jan, 05/2025) በሀገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከሌሊቱ 1:00 AM ጀምሮ ሥርዓተ ማኅሌቱና የቅዳሴ ቤቱ በዓል ስለሚከበር ከላይ በተጠቀሱት ታሪካዊ ቀናት የተዋሕዶ ልጆች ምዕመናን ሁላችሁም በቦታው (2912 King St Alexandria VA 22302) ተገኝታችሁ በዓሉን እንድታከብሩ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም ጥሪያችንን እናቀርባለን ::
ሰላመ እግዚአብሔር አይለየን
መልአከ ገነት ቀሲስ ጥላሁን አበበ
የደብሩ አስተዳዳሪ