“ነፃነት”
📌ለአንድ ቀን የሚቆየው የሥዕል ኤግዚብሽንና ጨረታ ህዳር 26 ይካሄዳል።
ሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ በቅርቡ በስዊድን ለሚያደርገው ህክምና ወጪን ለመሸፈን ነጻነት የተሰኘ የሥዕል ኤግዚብሽን ማዘጋጀቱን በዛሬው እለት በጎልደን ቱሊፕ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
ጋዜጠኛ ኤደን ገብረህይወት እና ጋዜጠኛ ራኬብ ሐብቴ በጋራ ባሰናዱት እና በመጪው ሐሙስ ሕዳር 26 ቀን 2017 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል ውስጥ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በላሊበላ አዳራሽ በሚካሄደው የሥእል አውደ- ርዕይና የሥዕል ጨረታ ፕሮግራም የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው የጥበብ ሰዎችና ሠአሊዎች ይገኛሉ ተብሏል።
ሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ ከ17 አመት ዕድሜው ጀምሮ አንኪሉዚንግ ስፖንዳላይተስ የተሰኘ አጥንት ውስጥ ያለ ፈሳሽን የሚያደርቅ ህመም አጋጥሞት ሙሉ በሙሉ ሰውነቱ እንዳይነቀሳቀስ ያደረገው ሲሆን በቅርቡ በስዊድን ሀገር ለሚያደርገው የጉልበት ንቅለ ህክምና ወጪን ለመሸፈን “ነጻነት” የተሰኘ የስዕል ኤግዚብሽን ተዘጋጅቷል።
ሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ እንደገለፀው ከዚህ የሥእል አውደ- ርዕይና የስእል ጨረታ ፕሮግራም የሚገኘው ገቢ በቅርቡ ስዊድን ሀገር ለሚያደርገው የጉልበት ንቅለተከላ የሚውል ሲሆን አጠቃላይ የህክምና ወጪው ሶስት ሚልየን ብር እንደሆነ ተገልጿል።
📌ለአንድ ቀን የሚቆየው የሥዕል ኤግዚብሽንና ጨረታ ህዳር 26 ይካሄዳል።
ሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ በቅርቡ በስዊድን ለሚያደርገው ህክምና ወጪን ለመሸፈን ነጻነት የተሰኘ የሥዕል ኤግዚብሽን ማዘጋጀቱን በዛሬው እለት በጎልደን ቱሊፕ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
ጋዜጠኛ ኤደን ገብረህይወት እና ጋዜጠኛ ራኬብ ሐብቴ በጋራ ባሰናዱት እና በመጪው ሐሙስ ሕዳር 26 ቀን 2017 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል ውስጥ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በላሊበላ አዳራሽ በሚካሄደው የሥእል አውደ- ርዕይና የሥዕል ጨረታ ፕሮግራም የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው የጥበብ ሰዎችና ሠአሊዎች ይገኛሉ ተብሏል።
ሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ ከ17 አመት ዕድሜው ጀምሮ አንኪሉዚንግ ስፖንዳላይተስ የተሰኘ አጥንት ውስጥ ያለ ፈሳሽን የሚያደርቅ ህመም አጋጥሞት ሙሉ በሙሉ ሰውነቱ እንዳይነቀሳቀስ ያደረገው ሲሆን በቅርቡ በስዊድን ሀገር ለሚያደርገው የጉልበት ንቅለ ህክምና ወጪን ለመሸፈን “ነጻነት” የተሰኘ የስዕል ኤግዚብሽን ተዘጋጅቷል።
ሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ እንደገለፀው ከዚህ የሥእል አውደ- ርዕይና የስእል ጨረታ ፕሮግራም የሚገኘው ገቢ በቅርቡ ስዊድን ሀገር ለሚያደርገው የጉልበት ንቅለተከላ የሚውል ሲሆን አጠቃላይ የህክምና ወጪው ሶስት ሚልየን ብር እንደሆነ ተገልጿል።
- See also: …