“ንስሩ ልጅ” የተሰኘ ፊልም ለእይታ ቀረበ።
በሱራፌል መልቲሚዲያ አማካኝነት የተሰናዳው “ንስሩ ልጅ” የተሰኘ አንድ ሰዓት ከሃያ ደቂቃ ርዝማኔ ያለው እና የቤተሰብ ፊልም በዓለም ሲኒማ ለእይታ መቅረብ ጀመረ።
በኢትዮጵያ ፊልም ኢንዱስተሪ ውስጥ የተለያዩ ፊልሞችን በድርሰት ፣ በዳይሬክቲንግ እና በኘሮዲወሲንግ ስራዎች መስክ ከፍተኛ አስተዋጾ እያደረገ በሚገኘው በደራሲና ዳይሬክተር ሱራፌል ኪዳኔ አማካኝነት የተዘጋጀው “ንስሩ ልጅ” ፊልም በትናንትናው እለት በዓለም ሲኒማ በይፋ ተመርቋል።
የፊልሙ ደራሲና ዳይሬክተር ሱራፌል ኪዳኔ በፊልም ምረቃው መርሐግብር ላይ እንገለጸው ስድስት አመት በላይ የወሰደው “ንስሩ ልጅ” ፊልም በብዙ ጥናት ላይ በመመርኮዝ በታዳጊ ልጆች እና ወላጆቻቸው ላይ ትኩረት በማደረግ ልጅን ከወላጅ ጋር በማቀራረብ መልካም ትውልድን ለመፈጠር እየተሰራ ባለው ስራ ላይ ተጨማሪ ግብአት እንዲሆን በማሰብ መዘጋጀቱን ገልጿል።
“ንስሩ ልጅ” ፊልም ለተከታዮቹ አራት ሳምንት ዘወትር እሁድ ከረፋዱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ በአለም ሲኒማ እና በቀጣይ በተለያዩ ትምህርት ቤቶች እና በተለያዩ ሲኒማ ቤቶች ለእይታ የሚቀርብ ሲሆን ወላጆች ከልጆቻቸው ጋር እንዲመለከቱት ደራሲ መልዕክት አስተላልፏል።
በሱራፌል መልቲሚዲያ አማካኝነት የተሰናዳው “ንስሩ ልጅ” የተሰኘ አንድ ሰዓት ከሃያ ደቂቃ ርዝማኔ ያለው እና የቤተሰብ ፊልም በዓለም ሲኒማ ለእይታ መቅረብ ጀመረ።
በኢትዮጵያ ፊልም ኢንዱስተሪ ውስጥ የተለያዩ ፊልሞችን በድርሰት ፣ በዳይሬክቲንግ እና በኘሮዲወሲንግ ስራዎች መስክ ከፍተኛ አስተዋጾ እያደረገ በሚገኘው በደራሲና ዳይሬክተር ሱራፌል ኪዳኔ አማካኝነት የተዘጋጀው “ንስሩ ልጅ” ፊልም በትናንትናው እለት በዓለም ሲኒማ በይፋ ተመርቋል።
የፊልሙ ደራሲና ዳይሬክተር ሱራፌል ኪዳኔ በፊልም ምረቃው መርሐግብር ላይ እንገለጸው ስድስት አመት በላይ የወሰደው “ንስሩ ልጅ” ፊልም በብዙ ጥናት ላይ በመመርኮዝ በታዳጊ ልጆች እና ወላጆቻቸው ላይ ትኩረት በማደረግ ልጅን ከወላጅ ጋር በማቀራረብ መልካም ትውልድን ለመፈጠር እየተሰራ ባለው ስራ ላይ ተጨማሪ ግብአት እንዲሆን በማሰብ መዘጋጀቱን ገልጿል።
“ንስሩ ልጅ” ፊልም ለተከታዮቹ አራት ሳምንት ዘወትር እሁድ ከረፋዱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ በአለም ሲኒማ እና በቀጣይ በተለያዩ ትምህርት ቤቶች እና በተለያዩ ሲኒማ ቤቶች ለእይታ የሚቀርብ ሲሆን ወላጆች ከልጆቻቸው ጋር እንዲመለከቱት ደራሲ መልዕክት አስተላልፏል።