የመምህር ሥዩም ጉልላት ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ።በመንበረ ፓትርያርክ …

Reading Time: < 1 minute
*
የመምህር ሥዩም ጉልላት ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ።

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የዜና ቤተ ክርስቲያን ጋዜጣ ምክትል አዘጋጅና በተለያዩ አህጉረ ስብከት ሰባኬ ወንጌል በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት መምህር ሥዩም ጉልላት ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዛሬ ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ.ም ተፈጸመ።

መምህር ሥዩም ጉልላት ሐምሌ 7 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በደረሰባቸው ድንገተኛ የመኪና አደጋ ምክንያት ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል።

መምህር ሥዩም ጉልላት በ1978 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ ሰላሌ ቀጸባ ማርያም በተባለ ሥፍራ የተወለዱ ሲሆን ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፣ በጅማ አበልቲ ኪዳነ ምሕረት ገዳም፣ ሰዋስዎ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ፣ በቅድስት ሥላሴ ዪኑቨርሲቲ በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እና በተለያዩ ማሰልጠኛ ተቋማት ትምህርታቸውን መከታተላቸው የሕይወት ታሪካቸው ያስረዳል።

Via ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
146370cookie-checkየመምህር ሥዩም ጉልላት ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ።በመንበረ ፓትርያርክ …

Share to...

Facebook
Telegram
WhatsApp
Twitter
Email
Print
ጌች ሐበሻ

ጌች ሐበሻ

ጌትነት ተመስገን (ጌች ሐበሻ) በማኀበራዊ ጉዳዮች እና ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመጻፍ ንቁ ተሳታፊ ነው።
ጌች ሐበሻ

ጌች ሐበሻ

ጌትነት ተመስገን (ጌች ሐበሻ) በማኀበራዊ ጉዳዮች እና ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመጻፍ ንቁ ተሳታፊ ነው።

Any Thought?

Be part of the Community! Comment, connect, spread some joy and let the fun begin!

YOU MAY ALSO LIKE