“የክብር ሽልማት”
…

የመጨረሻ ቀን የተቆረጠለት አርብ ግንቦት 9 2016 ዓ.ም በግዮን ግሮቭ ጋርደን በሚከናወን ታላቅ ሥነ ስርዓት አሸናፊዎች ይታወቃሉ ።

የክብር ሽልማት ከ 16ቱም ዘርፍ የተውጣጡ ዕጩዎች በዕለቱ ከ 11 ሰዓት ጀምሮ በግሮቭ ጋርደን ይታደማሉ።

በቃል መልቲሚዲያ አማካይነት ‹‹ክብር ሽልማት›› በሚል ሀሳብ ለደራሲዎችና ለሚዲያ ባለሙያዎች ሽልማት ለመስጠት ታላቅ ሀገራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወቃል፡፡
በዚህም መሰረት፣ የክብር ሽልማት አዘጋጆች ካለፈው ዓመት አንስቶ ባለሙያዎች፣ በድረገጽ እና በሌሎች የመገናኛ አውታሮች እንዲጠቆሙ ሲያደርጉ ነበር።

በሚዲያና በድርሰት ዘርፍ የተጠቆሙ ሰዎችን በድረገጽ ላይ በማውጣት ባለፉት ቀናት ዳኞችና ህዝብ እንዲመርጡ መደረጉ ይታወሳል፡፡
አጠቃላይ በ16 ዘርፎች በባለሙያዎችና በሕዝብ ድምጽ ሲሰጥባቸው የቆየ ሲሆን ከ300 በላይ ሰዎችም ተወዳድረው ከየዘርፉ 77 ሰዎች ወደ ፍጻሜው ዙር አልፈው ድምፅ ሲሰጥበት ነበር።
ከእያንዳንዱ ዘርፍ ከተጠቆሙ ሥራ እና ሠራተኞች ውስጥ ምርጥ 5ቱን ለመምረጥ ከህዝብ የተገኘን 40 ከመቶ ድምጽ እንዲሁም በዳኞች የተሰጠን 60 ከመቶ አንድ ላይ በማድረግ ክብር ሽልማት በ16 ዘርፎች ምርጥ አምስት ያላቸውን ባለሙያዎች ሚያዝያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

ተወዳዳሪዎች በ2015 ባለው የሥራ ውጤታቸው እንዲዳኙ ተደርጓል፡፡ ይህንንም ዕውን ለማድረግ በክብር ሽልማት ስር የተዋቀረው የጥናት ምርምር ክፍል የባለሙያዎችን የህይወት ታሪክ እንዲሁም ናሙና ስራዎችን በቋት ውስጥ በማጠራቀም ለዳኝነቱ ስራ ተገቢ መላ ዘይዶ የማወዳደሩን ስራ በተገቢው መልኩ አከናውኗል፡፡
የዳኝነት ሥራውም ፍጹም ምስጢራዊ በሆነ መልኩ እንዲከናወን ባለሙያዎችን ከሥራቸው አንጻር ብቻ በማየት ወደ ውድድሩ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡

ግንቦት 9 አርብ ዕለት ዝግጅታቸውን ጨርሰው በእለቱ ክቡራን እጩ ተወዳዳሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ባለሥልጣናት እና እንግዶች በተገኙበት አንደኛውን የክብር ሽልማት መርሐ ግብር ያከናውናሉ ዝግጅቱም በሀገሬ ቲቪ በአራዳ ሬድዮ ይተላለፋል ተብሏል ፡፡
event @yenevibe Yenevibe.com
…

የመጨረሻ ቀን የተቆረጠለት አርብ ግንቦት 9 2016 ዓ.ም በግዮን ግሮቭ ጋርደን በሚከናወን ታላቅ ሥነ ስርዓት አሸናፊዎች ይታወቃሉ ።

የክብር ሽልማት ከ 16ቱም ዘርፍ የተውጣጡ ዕጩዎች በዕለቱ ከ 11 ሰዓት ጀምሮ በግሮቭ ጋርደን ይታደማሉ።

በቃል መልቲሚዲያ አማካይነት ‹‹ክብር ሽልማት›› በሚል ሀሳብ ለደራሲዎችና ለሚዲያ ባለሙያዎች ሽልማት ለመስጠት ታላቅ ሀገራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወቃል፡፡
በዚህም መሰረት፣ የክብር ሽልማት አዘጋጆች ካለፈው ዓመት አንስቶ ባለሙያዎች፣ በድረገጽ እና በሌሎች የመገናኛ አውታሮች እንዲጠቆሙ ሲያደርጉ ነበር።

በሚዲያና በድርሰት ዘርፍ የተጠቆሙ ሰዎችን በድረገጽ ላይ በማውጣት ባለፉት ቀናት ዳኞችና ህዝብ እንዲመርጡ መደረጉ ይታወሳል፡፡
አጠቃላይ በ16 ዘርፎች በባለሙያዎችና በሕዝብ ድምጽ ሲሰጥባቸው የቆየ ሲሆን ከ300 በላይ ሰዎችም ተወዳድረው ከየዘርፉ 77 ሰዎች ወደ ፍጻሜው ዙር አልፈው ድምፅ ሲሰጥበት ነበር።
ከእያንዳንዱ ዘርፍ ከተጠቆሙ ሥራ እና ሠራተኞች ውስጥ ምርጥ 5ቱን ለመምረጥ ከህዝብ የተገኘን 40 ከመቶ ድምጽ እንዲሁም በዳኞች የተሰጠን 60 ከመቶ አንድ ላይ በማድረግ ክብር ሽልማት በ16 ዘርፎች ምርጥ አምስት ያላቸውን ባለሙያዎች ሚያዝያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

ተወዳዳሪዎች በ2015 ባለው የሥራ ውጤታቸው እንዲዳኙ ተደርጓል፡፡ ይህንንም ዕውን ለማድረግ በክብር ሽልማት ስር የተዋቀረው የጥናት ምርምር ክፍል የባለሙያዎችን የህይወት ታሪክ እንዲሁም ናሙና ስራዎችን በቋት ውስጥ በማጠራቀም ለዳኝነቱ ስራ ተገቢ መላ ዘይዶ የማወዳደሩን ስራ በተገቢው መልኩ አከናውኗል፡፡
የዳኝነት ሥራውም ፍጹም ምስጢራዊ በሆነ መልኩ እንዲከናወን ባለሙያዎችን ከሥራቸው አንጻር ብቻ በማየት ወደ ውድድሩ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡

ግንቦት 9 አርብ ዕለት ዝግጅታቸውን ጨርሰው በእለቱ ክቡራን እጩ ተወዳዳሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ባለሥልጣናት እና እንግዶች በተገኙበት አንደኛውን የክብር ሽልማት መርሐ ግብር ያከናውናሉ ዝግጅቱም በሀገሬ ቲቪ በአራዳ ሬድዮ ይተላለፋል ተብሏል ፡፡
event @yenevibe Yenevibe.com