የቴሌግራም መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ በ5 ሚሊየን ዩሮ ዋስ ተፈታዱሮቭ በግል ጄት ከአዘርባጃን ተነስቶ ፓሪ…

Reading Time: < 1 minute
*
የቴሌግራም መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ በ5 ሚሊየን ዩሮ ዋስ ተፈታ

ዱሮቭ በግል ጄት ከአዘርባጃን ተነስቶ ፓሪስ ባረፈበት ወቅት በፈረንሳይ መንግስት በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ከአራት ቀናት የእስር ጊዜ በኋላ ትናንት ምሽት ፍርድ ቤት ቀርቧል፡፡

በፍርድ ቤቱ ውሳኔ መሰረትም ዱሮቭ በ5 ሚሊየን ዩሮ ዋስ የተፈታ ቢሆንም የተጠረጠረበት የቴሌግራም የመረጃ ደህንነት ወንጀል ተጣርቶ እስከሚረጋገጥ ከፈረንሳይ እንዳይወጣ መከልከሉ ነው የተገለፀው፡፡

በድሮቭ ላይ ከቀረቡ ክሶች መካከል ህገ ወጥ ግብይት፣ ህገ ወጥ ግለሰቦች ቴግራምን ለወንጀል እንዲጠቀሙመተባበር፣ አስተማማኝ ያልሆነ የቴሌግራም አስተዳደር፣ የእፅ ዝውውር እና ለህፃናት ያልተፈቀድ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን መልቀቅ የሚሉት ይገኙበታል፡፡

በተጨማሪም በቴሌግራም መተግበሪያ ላይ ምርመራ እንዲደረግ አለመፍቀድ የሚል ክስም ቀርቦበታል ሲል አር ቲ ዘግቧል፡፡
151620cookie-checkየቴሌግራም መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ በ5 ሚሊየን ዩሮ ዋስ ተፈታዱሮቭ በግል ጄት ከአዘርባጃን ተነስቶ ፓሪ…

Share to...

Facebook
Telegram
WhatsApp
Twitter
Email
Print
ጌች ሐበሻ

ጌች ሐበሻ

ጌትነት ተመስገን (ጌች ሐበሻ) በማኀበራዊ ጉዳዮች እና ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመጻፍ ንቁ ተሳታፊ ነው።
ጌች ሐበሻ

ጌች ሐበሻ

ጌትነት ተመስገን (ጌች ሐበሻ) በማኀበራዊ ጉዳዮች እና ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመጻፍ ንቁ ተሳታፊ ነው።

Any Thought?

Be part of the Community! Comment, connect, spread some joy and let the fun begin!

YOU MAY ALSO LIKE