ተወዳጁ ድምፃዊ አህመድ ሁሴን(ማንጁስ) የመጀመርያ አልበሙን ጥር 16 ይለቀቃል ተባለ፡፡
ተወዳጁ ድምፃዊ አልበሙን በቅርብ ቀን ማለትም ጥር 16/2017 ለመልቀቅ ዝግጅቱን መጨረሱን ገልጿል፡፡ ድምፃዊ አህመድ ሁሴን(ማንጁስ)በፋና ላምሮት ውድድር በአምስተኛው ምዕራፍ አሸናፊ እና የአሸናፊዎች አሸናፊ የሆነ ከዛም የተለያዩ ነጠላ ሙዚቃዎች ለአድማጭ አድርሷል በተለይ “ደሴ ላይ ቤቷ” በህዝብ ዘንድ በይበልጥ ይታወቃል፡፡ አሁን ደሞ የበኩር አልበሙን “አልጣሽ” የተሰኘ ስያሜ ያለው ሲሆን ወደ 11 የሙዚቃ ክሮች ተካተዋል፡፡
በዚህ አልበም ተወዳጅ ወጣት እና አንጋፋ የሙዚቃ ባለሞያዎች የተሳተፉ ሲሆን በግጥም ይልማ ገብረዓብ ፣ ናትናኤል ግርማቸው ፣ መሰለ ጌታሁን ፣ ተስፋ ብርሀን በዜማው አበበ ብርሀኔ ፣ አቤል ሙሉጌታ ፣ አህመድ ተሾመ(ዲንቢ)) በቅንብር አበጋዝ ክብረ ወርቅ ሽዎታ አብዛኛው ያቀናበረ ሲሆን ቀሪውን አቤል ጳውሎስ በጋራ ሰርተውታል፡፡ በማስተሪን እና ሚክስ በታላቁ አበጋዝ ክብረ ወርቅ እንደ ተሰራም ተጠቁሟል፡፡
ጥር 16 በናሆም ሪከርድስ በኩል የሙዚቃ አድማጮች ሁሉ ይደርሳል፡፡
via yenevibe
(ተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ)
ተወዳጁ ድምፃዊ አልበሙን በቅርብ ቀን ማለትም ጥር 16/2017 ለመልቀቅ ዝግጅቱን መጨረሱን ገልጿል፡፡ ድምፃዊ አህመድ ሁሴን(ማንጁስ)በፋና ላምሮት ውድድር በአምስተኛው ምዕራፍ አሸናፊ እና የአሸናፊዎች አሸናፊ የሆነ ከዛም የተለያዩ ነጠላ ሙዚቃዎች ለአድማጭ አድርሷል በተለይ “ደሴ ላይ ቤቷ” በህዝብ ዘንድ በይበልጥ ይታወቃል፡፡ አሁን ደሞ የበኩር አልበሙን “አልጣሽ” የተሰኘ ስያሜ ያለው ሲሆን ወደ 11 የሙዚቃ ክሮች ተካተዋል፡፡
በዚህ አልበም ተወዳጅ ወጣት እና አንጋፋ የሙዚቃ ባለሞያዎች የተሳተፉ ሲሆን በግጥም ይልማ ገብረዓብ ፣ ናትናኤል ግርማቸው ፣ መሰለ ጌታሁን ፣ ተስፋ ብርሀን በዜማው አበበ ብርሀኔ ፣ አቤል ሙሉጌታ ፣ አህመድ ተሾመ(ዲንቢ)) በቅንብር አበጋዝ ክብረ ወርቅ ሽዎታ አብዛኛው ያቀናበረ ሲሆን ቀሪውን አቤል ጳውሎስ በጋራ ሰርተውታል፡፡ በማስተሪን እና ሚክስ በታላቁ አበጋዝ ክብረ ወርቅ እንደ ተሰራም ተጠቁሟል፡፡
ጥር 16 በናሆም ሪከርድስ በኩል የሙዚቃ አድማጮች ሁሉ ይደርሳል፡፡
via yenevibe
(ተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ)