ሻርኮች በተደረገላቸው ምረምራ ኮኬይን ተገኘ
በብራዚል ባሕር ዳርቻ ያሉ ሻርኮች በተደረገላቸው ምርመራ ሰውነታቸው ውስጥ ኮኬይን መገኘቱን ተመራማሪዎች ገለጹ።
የባሕር ተመራማሪዎች 13 ሻርፖንስ በመባል የሚታወቁ ሻርኮች ላይ ምርመራ አድርገዋል። እነዚህ የዓሣ ዓይነቶች በሪዮ ደ ጀኔሮ ባሕር ዳርቻ አቅራቢያ የተገኙ ናቸው።
በጡንቻቸው እና ጉበታቸው ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው ኮኬይን እንደተገኘም ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም በሌሎች የባሕር ውስጥ እንስሳት ላይ ከተገኘው የኮኬይን መጠን ጋር ሲነጻጸር ይሄኛው በ100 እጥፍ እንደሚልቅ ተገልጿል።
ኦስዋልዶ ክሩዝ ፋውንዴሽን በተባለ ተቋም የተሠራው ጥናት በሻርኮች ሰውነት ውስጥ ኮኬይን ሲገኝ የመጀመሪያ ጊዜ ነው።
bbc amharic
በብራዚል ባሕር ዳርቻ ያሉ ሻርኮች በተደረገላቸው ምርመራ ሰውነታቸው ውስጥ ኮኬይን መገኘቱን ተመራማሪዎች ገለጹ።
የባሕር ተመራማሪዎች 13 ሻርፖንስ በመባል የሚታወቁ ሻርኮች ላይ ምርመራ አድርገዋል። እነዚህ የዓሣ ዓይነቶች በሪዮ ደ ጀኔሮ ባሕር ዳርቻ አቅራቢያ የተገኙ ናቸው።
በጡንቻቸው እና ጉበታቸው ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው ኮኬይን እንደተገኘም ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም በሌሎች የባሕር ውስጥ እንስሳት ላይ ከተገኘው የኮኬይን መጠን ጋር ሲነጻጸር ይሄኛው በ100 እጥፍ እንደሚልቅ ተገልጿል።
ኦስዋልዶ ክሩዝ ፋውንዴሽን በተባለ ተቋም የተሠራው ጥናት በሻርኮች ሰውነት ውስጥ ኮኬይን ሲገኝ የመጀመሪያ ጊዜ ነው።
bbc amharic