” ምን ሆኛለሁ ? መጽሐፍ የትዕግስት ዋልተንጉስ አዲስ መፅሐፍ

የወራት ድካም ነው ። እኔን በግል ለቀናት ካልተገደድኩ ከቤት እንዳልወጣ ያደረገኝና ብዙ ማህበራዊ ግንኙነቴን ያቋረጠብኝ ስራ ነው ። ድካማችን ለመልካም በመሆኑ ሁለታችንም ደስተኞች ነን ። አንድ ሰው በሕይወት ዘመኑ ፣ ከማለፉ በፊት ከሚሰራቸው ስራዎች መሀል አንዱ ( ለትዕግሥት ዋልተንጉሥ እና ለእኔ ) ይህ ” ምን ሆኛለሁ ? ” ብለን የሰየምነው መጽሐፍ ነው ። ” ምን ሆኛለሁ ? ” ለትዕግሥት ዋልተንጉሥ የመጀመሪያዋ ፣ ለእኔ ደግሞ 7ኛ ስራችን ነው ። የሁለታችን ጥምረት ትልቅ ስራ የፈጠረ ይመስለኛል ።
የስነልቦና ባለሙያዋ ትዕግሥት ዋልተንጉሥ ከ15 ዓመት በላይ በምክክር አገልግሎት ላይ ሰርታለች ። በ” እርቅ ማዕድ ” የሬዲዮ ፕሮግራም እንዲሁም በEBS ቴሌቪዥን ” እንመካከር ” ፕሮግራምን አዘጋጅታለች ። እኔ መጠየቅ ፣ ሀሳቦችን የተቻለኝን ያህል ውስጥ ድረስ ገብቼ ለመረዳት መሞከር ፣ ቀላል እና ልብ ደረስ አማርኛን መጻፍ እችላለሁ ። ሁለታችን ” ምን ሆኛለሁ ? ” ን ከማንም ቀድመን ራሳችን ወደነዋል ። እኔ በግሌ እስካሁን በጽሑፍ ከሰራኋቸው መጻሕፍትም ፣ ድራማዎችም ሁሉ የእኔ ለምለው ሕዝብ የማበረክተው ትልቁ ስራ ይህ በቅርቡ የሚወጣው መጽሐፍ እንደሚሆን አፌን ሞልቼ መናገር እችላለሁ ። በቀላሉ የምማልል እና በራሴ ስራ የምመሰጥ ሰው አይደለሁም ። ” ምን ሆኛለሁ ? ” ግን እንደዚያ አይነት ስሜት እንዲሰማኝ አድርጎኛል ። ይሄ ስሜት ነገ እናንተ ላይ እንደሚጋባ አምናለሁ ።

” ምን ሆኛለሁ ? ” ን በመስራቱ ሂደት ለእኔ ትልቁ የስነልቦና ት/ቤት የገባሁ ያህል ተሰምቶኛል ። የራሴን ፣ የቤተሰቤን ፣ የወዳጆቼን ፣ በቅርብም በርቀትም የማያቸውን ኢትዮጵያውያን ፣ ዝነኛ ሰዎችን ፣ ፖለቲከኞችን ፣ የእውቀት ሰዎችን ለየት ያሉ ባህርያት ለመረዳት ፣ ምክንያታቸውን ለመገመት ፣ ሰውን በሚመለከት ፈራጅ ላለመሆን ፣ ሰው ማለት አሁን አብሮን የሚኖረው ወይም የሚሰራው ብቻ ሳይሆን የእስከዛሬውን – ይበልጡንም ልጅነቱንና አስተዳደጉን እንደሆነ እንድገነዘብ ረድቶኛል ።

” ይህን መጽሐፍ የሚያነቡ ሰዎች ራሳቸውንና የሚያውቋቸውን ሁሉ እንዲፈትሹ ፣ እንዲረዱና እንዲያግዙ እጅጉን ይረዳቸዋል ። ፖሊሲ አውጪዎች ለፖሊሲ ጥናት ይጠቅማቸዋል ብዬ አምናለሁ ። ” ይህን ያለው አንድ የአዕምሮ ሀኪም ነው ። ይህን አስተያየቱን በመጽሐፉ ላይ ታገኙታላችሁ ። ዛሬ ላይ ከሚታይ የሰው ባህሪ ተነስተን ” እገሌ ማለት እንዲህ ነው ። ይህን ያደረገው ሆን ብሎ እኛን /እገሌን ለመጉዳት ነው ” እንላለን ። ከሂደቱ ይልቅ የመጨረሻ ውጤቱ ያሳስበናል ። ማንም ከባዶ ሜዳ ተነስቶ ምንም እንደማያደርግ ነው የስነልቦና ሰዎች የሚያምኑት ።

በተለይ አሁን ባለንበት ጊዜ ” ምን ሆኛለሁ ? ” መጽሐፍ እጅጉን ያስፈልጋል ። መንግሥት ወይም ሌሎች መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት በሚሊዮን ቅጂ አባዝተው በየቤቱ ቢያዳርሱና ልክ አሽከርካሪዎች የአሽከርካሪ ቀበቶ ተገደው አስረው ለሕይወታቸው ጠቃሚ እንደሆነው ከዚያ በላይ ፋይዳ ያለው ስራ እንደሆነ አምንበታለሁ ። አሁን ጉዳዩ የራስን ስራ ማስተዋወቅ ፣ ብዙ ቅጂ መሸጥና ከዚያ ገንዘብ ማግኘት አይደለም ዋናው ዓላማ ። እርግጥ ነው ብዙ ሲሸጥ በዚያው ልክ የገንዘብ ጥቅሙም አለ ። ይሁንና ግን ሰዎች መጽሐፉን ከገዛ ወዳጃቸው ተውሰው አንብበው ” በቀጣይም ቤቴ ሊኖር የሚገባ መጽሐፍ ነው ” ብለው ሲያምኑ ቢገዙ እሱም ይስማማናል ። ብቻ ” ምን ሆኛለሁ ? ” ከማንም ቤት ባይጠፋ ምኞታችን ነው ።

ትዕግሥት ዋልተንጉሥ እና ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
በብር 1,000.0 ሦስት መጻሕፍት መግዛት የሚቻል ሲሆን ከዚያ በላይ የምትገዙ እያንዳንዱን ሺህ በሦስት በማባዛት የምታገኙትን መጻሕፍት ቁጥር ማግኘት ይቻላል ። ወዳጅ ዘመዶች በዚህ ዘመቻ በትጋት እንድትሳተፉ እንጠይቃለን ። የብዙሀን መገናኛ ባለሙያዎች ፣ ፌስቡከሮችና ቲክቶከሮች መጽሐፉን በማስተዋወቅ አግዙን ። የምታግዙት መልካም ስራን እንደሆነ እኛን እመኑ ። ከታች ባለው የባንክ ሂሳብ ገንዘቡን ገቢ ካደረጋቾሁ በኋላ ያስገባችሁበትን ‘ ስክሪን ሾት ‘ አድርጋችሁ እንድትልኩልኝ እጠይቃለሁ ። መግዛት የቻላችሁም ያልቻላችሁ መልዕክቱን በማጋራት ቸባበሩን ።

1000183007592
Tewodros Teklearegay
CBE
#SHARE በማድረግ ዘመቻውን ይደግፉ !!!

የወራት ድካም ነው ። እኔን በግል ለቀናት ካልተገደድኩ ከቤት እንዳልወጣ ያደረገኝና ብዙ ማህበራዊ ግንኙነቴን ያቋረጠብኝ ስራ ነው ። ድካማችን ለመልካም በመሆኑ ሁለታችንም ደስተኞች ነን ። አንድ ሰው በሕይወት ዘመኑ ፣ ከማለፉ በፊት ከሚሰራቸው ስራዎች መሀል አንዱ ( ለትዕግሥት ዋልተንጉሥ እና ለእኔ ) ይህ ” ምን ሆኛለሁ ? ” ብለን የሰየምነው መጽሐፍ ነው ። ” ምን ሆኛለሁ ? ” ለትዕግሥት ዋልተንጉሥ የመጀመሪያዋ ፣ ለእኔ ደግሞ 7ኛ ስራችን ነው ። የሁለታችን ጥምረት ትልቅ ስራ የፈጠረ ይመስለኛል ።
የስነልቦና ባለሙያዋ ትዕግሥት ዋልተንጉሥ ከ15 ዓመት በላይ በምክክር አገልግሎት ላይ ሰርታለች ። በ” እርቅ ማዕድ ” የሬዲዮ ፕሮግራም እንዲሁም በEBS ቴሌቪዥን ” እንመካከር ” ፕሮግራምን አዘጋጅታለች ። እኔ መጠየቅ ፣ ሀሳቦችን የተቻለኝን ያህል ውስጥ ድረስ ገብቼ ለመረዳት መሞከር ፣ ቀላል እና ልብ ደረስ አማርኛን መጻፍ እችላለሁ ። ሁለታችን ” ምን ሆኛለሁ ? ” ን ከማንም ቀድመን ራሳችን ወደነዋል ። እኔ በግሌ እስካሁን በጽሑፍ ከሰራኋቸው መጻሕፍትም ፣ ድራማዎችም ሁሉ የእኔ ለምለው ሕዝብ የማበረክተው ትልቁ ስራ ይህ በቅርቡ የሚወጣው መጽሐፍ እንደሚሆን አፌን ሞልቼ መናገር እችላለሁ ። በቀላሉ የምማልል እና በራሴ ስራ የምመሰጥ ሰው አይደለሁም ። ” ምን ሆኛለሁ ? ” ግን እንደዚያ አይነት ስሜት እንዲሰማኝ አድርጎኛል ። ይሄ ስሜት ነገ እናንተ ላይ እንደሚጋባ አምናለሁ ።

” ምን ሆኛለሁ ? ” ን በመስራቱ ሂደት ለእኔ ትልቁ የስነልቦና ት/ቤት የገባሁ ያህል ተሰምቶኛል ። የራሴን ፣ የቤተሰቤን ፣ የወዳጆቼን ፣ በቅርብም በርቀትም የማያቸውን ኢትዮጵያውያን ፣ ዝነኛ ሰዎችን ፣ ፖለቲከኞችን ፣ የእውቀት ሰዎችን ለየት ያሉ ባህርያት ለመረዳት ፣ ምክንያታቸውን ለመገመት ፣ ሰውን በሚመለከት ፈራጅ ላለመሆን ፣ ሰው ማለት አሁን አብሮን የሚኖረው ወይም የሚሰራው ብቻ ሳይሆን የእስከዛሬውን – ይበልጡንም ልጅነቱንና አስተዳደጉን እንደሆነ እንድገነዘብ ረድቶኛል ።

” ይህን መጽሐፍ የሚያነቡ ሰዎች ራሳቸውንና የሚያውቋቸውን ሁሉ እንዲፈትሹ ፣ እንዲረዱና እንዲያግዙ እጅጉን ይረዳቸዋል ። ፖሊሲ አውጪዎች ለፖሊሲ ጥናት ይጠቅማቸዋል ብዬ አምናለሁ ። ” ይህን ያለው አንድ የአዕምሮ ሀኪም ነው ። ይህን አስተያየቱን በመጽሐፉ ላይ ታገኙታላችሁ ። ዛሬ ላይ ከሚታይ የሰው ባህሪ ተነስተን ” እገሌ ማለት እንዲህ ነው ። ይህን ያደረገው ሆን ብሎ እኛን /እገሌን ለመጉዳት ነው ” እንላለን ። ከሂደቱ ይልቅ የመጨረሻ ውጤቱ ያሳስበናል ። ማንም ከባዶ ሜዳ ተነስቶ ምንም እንደማያደርግ ነው የስነልቦና ሰዎች የሚያምኑት ።

በተለይ አሁን ባለንበት ጊዜ ” ምን ሆኛለሁ ? ” መጽሐፍ እጅጉን ያስፈልጋል ። መንግሥት ወይም ሌሎች መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት በሚሊዮን ቅጂ አባዝተው በየቤቱ ቢያዳርሱና ልክ አሽከርካሪዎች የአሽከርካሪ ቀበቶ ተገደው አስረው ለሕይወታቸው ጠቃሚ እንደሆነው ከዚያ በላይ ፋይዳ ያለው ስራ እንደሆነ አምንበታለሁ ። አሁን ጉዳዩ የራስን ስራ ማስተዋወቅ ፣ ብዙ ቅጂ መሸጥና ከዚያ ገንዘብ ማግኘት አይደለም ዋናው ዓላማ ። እርግጥ ነው ብዙ ሲሸጥ በዚያው ልክ የገንዘብ ጥቅሙም አለ ። ይሁንና ግን ሰዎች መጽሐፉን ከገዛ ወዳጃቸው ተውሰው አንብበው ” በቀጣይም ቤቴ ሊኖር የሚገባ መጽሐፍ ነው ” ብለው ሲያምኑ ቢገዙ እሱም ይስማማናል ። ብቻ ” ምን ሆኛለሁ ? ” ከማንም ቤት ባይጠፋ ምኞታችን ነው ።

ትዕግሥት ዋልተንጉሥ እና ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
በብር 1,000.0 ሦስት መጻሕፍት መግዛት የሚቻል ሲሆን ከዚያ በላይ የምትገዙ እያንዳንዱን ሺህ በሦስት በማባዛት የምታገኙትን መጻሕፍት ቁጥር ማግኘት ይቻላል ። ወዳጅ ዘመዶች በዚህ ዘመቻ በትጋት እንድትሳተፉ እንጠይቃለን ። የብዙሀን መገናኛ ባለሙያዎች ፣ ፌስቡከሮችና ቲክቶከሮች መጽሐፉን በማስተዋወቅ አግዙን ። የምታግዙት መልካም ስራን እንደሆነ እኛን እመኑ ። ከታች ባለው የባንክ ሂሳብ ገንዘቡን ገቢ ካደረጋቾሁ በኋላ ያስገባችሁበትን ‘ ስክሪን ሾት ‘ አድርጋችሁ እንድትልኩልኝ እጠይቃለሁ ። መግዛት የቻላችሁም ያልቻላችሁ መልዕክቱን በማጋራት ቸባበሩን ።

1000183007592
Tewodros Teklearegay
CBE
#SHARE በማድረግ ዘመቻውን ይደግፉ !!!