የወደቁትን አንሱ የነዳያን መርጃ ማህበር የአረጋውያን የህክምና ማዕከል ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ::

Reading Time: < 1 minute

ማህበሩ ለአረጋውያን የህክምና ማዕከል ለመገንባትና በአረጋውያን ሕክምና ዙርያ ሐኪሞች የሚሰለጥኑበትን ተቋም ለመመስረት አላማ ይዞ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ እንደሆነ በማህበሩ የፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ አቶ ግርማ ገብረስላሴ  ለአራዳ ኤፍኤም ገልፀዋል::

የወደቁትን አንሱ የነዳያን መርጃ ማህበር በዛሬ ዕለት 25ኛ ዓመት በዓሉን አስመልክቶም የተለያዩ መርሃ-ግብሮችን ማዘጋጀቱን አሳውቋል::

ከነገ በስትያ በብሔራዊ ሙዝየም የድርጅቱን የ25 ዓመታት ጉዞ የሚያሳይ የፎቶግራፍ አውድርዕይ ለእይታ ክፍት የሚያደርግ ሲሆን ህዳር 9/2016 ዓ.ም. ደግሞ የገቢ ማሰባሰቢያ ያከናውናል::

ማህበሩ እንጦጦ ኪዳነምህረት አካባቢ ለ18 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቶ በአሁኑ ወቅት አርባ አንድ ኢየሱስ አካባቢ በሚገኝ ስፍራ እስከ 200 የሚደርሱ ዜጎችን እየረዳ ይገኛል::

@enqu(እንቁጣጣሽ ኃ/ማርያም )
61290cookie-checkየወደቁትን አንሱ የነዳያን መርጃ ማህበር የአረጋውያን የህክምና ማዕከል ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ::

Share to...

Facebook
Telegram
WhatsApp
Twitter
Email
Print
ጌች ሐበሻ

ጌች ሐበሻ

ጌትነት ተመስገን (ጌች ሐበሻ) በማኀበራዊ ጉዳዮች እና ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመጻፍ ንቁ ተሳታፊ ነው።
ጌች ሐበሻ

ጌች ሐበሻ

ጌትነት ተመስገን (ጌች ሐበሻ) በማኀበራዊ ጉዳዮች እና ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመጻፍ ንቁ ተሳታፊ ነው።

Any Thought?

Be part of the Community! Comment, connect, spread some joy and let the fun begin!

YOU MAY ALSO LIKE