ጨረታን ዲጂታል መልኩ የሚያቀርብ ፕላትፎርም ሊቀርብ ነው።

Reading Time: < 1 minute

በጨረታ ሂደት ላይ ከጉቦ እና ከመሰል የስነምግባር ችግሮች ጋር ተያይዞ የሚነሱ ቅሬታዎችን ያቃልላል የተባለው ይህ አሰራር የሰዎችን ንክኪ በእጅጉ እንደሚቀንስ ተሰምቷል!

ኦክሽን ኢትዮጵያ በተባለ ተቋም የተዋወቀው አሰራሩ የመንግስት ተቋማት፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ አለማቀፍ ድርጅቶች እና የግል ድርጅቶች እንዲሁም ግለሰቦች በጨረታ መሸጥ የፈልጉትን ንብረቶች በዲታጂታል መንገድ ቀላልና ምቹ ሆኖ ለተጫራቾች ተደራሽ እንዲሆን የሚያስችል መሆኑ ነው የተነገረው፡፡

እንዲሁም ተጠቃሚዎች የትም መሄድ ሳይጠበቅባቸው ጊዜና ገንዘባቸውን ሣያባክኑ ካሉበት ቦታ ብቻ ሆነው በስልካቸው ወይም በኮምፒዉተራቸው ጨረታን መጫረት ያስ4ችላል ተብሏል

በመንግስት መስሪያ ቤቶችም ሆነ በግል ተቋማት ቀድሞ ይከናወን የነበረው የጨረታ ሂደት እጅግ አድካሚ፣ ጊዜና ገንዘብን የሚያባክን ግልፅ ያልሆነና የተደራሽነት ዉስንነት ያለበት በመሆኑ እነዚህን ችግሮች በመቅረፍ ሚና ይኖረዋል ነው የተባለው፡፡
54420cookie-checkጨረታን ዲጂታል መልኩ የሚያቀርብ ፕላትፎርም ሊቀርብ ነው።

Share to...

Facebook
Telegram
WhatsApp
Twitter
Email
Print

Any Thought?

Be part of the Community! Comment, connect, spread some joy and let the fun begin!

YOU MAY ALSO LIKE